እሁድ እለት በተካሄደው የሪዮ ኦሎምፒክ የማራቶን ውድድር ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው የ26 ዓመቱ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በሪዮ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያ ይልቅ የውድድር መስመሩን ሲያጠናቅቅ፤ ያሳየው ሁለት እጆቹን የማጠላለፍ ምልክት ነው።
የ26 ዓመቱ ፈይሳ ሌሊሳ በትናንትናው በሪዮ ኦሎምፒክ የወንዶች ማራቶን የብር ሜዳልያ ያሸነፈበትን ሩጫ አጠናቆ ሲገባ በኦሮሞ ተቃውሞ ጊዜ የተጀመረውና በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ የተቃውሞ ምልክት የሆነውን እጅ ማጣመር ምልክት እያሳየ ገብቷል።
ዓርብ፤ ነኀሴ 13/2008 ዓ.ም ችሎት ፊት ይቀርባሉ ተብለው ሲጠበቁ የነበሩት ከወልቃይት ሕዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴ መሪዎች አንድ የሆኑት ኮሎሌል ደመቀ ዘውዴ ለሁለተኛ ጊዜ ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡
ጎንደር ከተማ ውስጥ አንድ የሃያ አራት ዓመት ወጣት ዛሬ በፀጥታ ኃይሎች መገደሉን ቤተሰቦቹ ገለጹ። የተገደለበት ምክንያትም “ነጭ ቲ-ሸርት በመልበሱ ነው” ብለዋል። የክልሉ መንግሥት ቃል አቀባይ ግን የወጣቱን መገደል አረጋግጠው የተገደለው ግን “በልብሱ ምክንያት አይደለም” ብለዋል፡፡
አቶ ሆራ ፈጂሳ የተባሉ ግለስብ መገደላቸውን ባለቤታቸውም ከአራስ ልጇ ጋር በእስር ቤት እንደምትገኝ ነዋሪዎች ገለጹ።
ኢትዮጵያ አስከፊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን በመጠቀስ ከቀውሱ ለመውጣት ኢሕአዴግ ከስልጣን ወርዶ የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም የሚጠይቁ ወገኖች አሉ።
ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በኢትዮጵያ በሳምንቱ መጨረሻ በተካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎች በአማራና በኦሮሚያ ክልል፤ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ በቀጥታ በተተኮሰ ጥይት ወደ 100 የሚጠጉ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን እየገለጹ ነው።
በዛሬው ዕለት በጎንደር ከተማ በተቀሰቀ ግጭት የሰው ሕይወት ጠፋ። የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እስካሁን የአራት ሰው ሕይወት ጠፍቷል ሲሉ የክልሉ መንግሥት እስካሁን ባለን መረጃ የጠፋው የአንድ ሰው ሕይወት ነው ብሏል።
በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲካሄድ የነበረው ተቃውሞ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በድጋሚ ማገርሸቱንና የሰባትና የ13 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሕፃናትን ጨምሮ በርካቶች እየተገደሉ መሆኑን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ። “ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓመት ልጄ አስክሬን እቤት ጠበቀኝ” ያሉ የአወዳይ ከተማ ነዋሪም ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
ሐምሌ አምስት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት ሶስት ቀናት በጎንደር ከተማ የተነሳውን ግጭት ተከትሎ በጎንደርና በደባርቅ በደረሰው ንብረት ውድመት በተደረገው ማጣራት በአጠቃላይ በጎንደር የ139 በደባርቅ ደግሞ የሦስት ኢትዮጵያውያን ንብረት በተለያየ ደረጃ መውደሙን የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ዳይሬክተር አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናገሩ። ይህንን ቁጥር ዘርዝረው በማብራራት ወደ አንድ ብሔር ያደላ ጥቃት እንዳልተፈፀመ ተናግረዋል።
ጎንደር ከተማ ውስጥ የተቃውሞ ትዕይንተ-ህዝብ ያደረጉ ዜጎች የታሠሩ የወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ ኮሜቴ አባላት እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
የዘንድሮዋ ወ/ት ኢትዮጵያ በዩናይትድ ስቴትስ በትውልድ ስሟ ሔለን ወርቁ አሁን ደግሞ ሔለን ኬነርድ ትባላለች። የ29 ዓመት ወጣት ስትሆን፤ የተወለደችው ሆለታ ከተማ ነበር።
የአምባሰልን ቅኝት በድምጿ ስትጫወተው የተደመሙ የሙዚቃ ባለሞያዎች "አምባሰልን ከተራራው በላይ ያገነነች"ይሏታል። የወሎ ዩኒቨርስቲ ደግሞ ለዚች እንቁ ድምፃዊ የክብር ዶክትሬት ሰጥቷታል። እንሷም “አንባሰልንማ ከእኔ በላይ የተጫወተው….” ትላለች- ድምፃዊት ማሪቱ ለገሰ።
አሜሪካውያን መራጮች ዶናልድ ትራምፕ በተወዳዳሪነት ሲቀርብ የተገረሙትን ያህል በማንም ተገርመው የሚያውቁ አይመስልም።
የወልቃይት የአማራ ሕዝብ ማንነት ጥያቄን ለማዳፈን ሰዎች ከያሉበት እየታሠሩ እንደሆነ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጪዎ ይናገራሉ። በሰሞኑ ጉዳይ ላይ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በትናንትናው ዕለት ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል። ጽዮን ግርማ ነች ያነጋገረቻቸው።
የወልቃይት የአማራ ሕዝብ ማንነት ጥያቄን ለማዳፈን ሰዎች ከያሉበት እየታሠሩ እንደሆነ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጪዎ ይናገራሉ። በሰሞኑ ጉዳይ ላይ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ቃለ ምልልስ ሰጥተዋል። ጽዮን ግርማ ነች ያነጋገረቻቸው።(ሙሉው ቃለ ምልልስ ነገ (ቅዳሜ) ምሽት ይቀርባል)።
ተጨማሪ ይጫኑ