ወግ ኮፌ፣ ‘ቁምነገር እና ቡና የሚቀዱበት’ ቡና ቤት -አጭር ዳሰሳ

ቁምነገር እና ቡና የሚቀዱበት የመሃል አዲስ አበባ ቡና ቤት ፣ ‘ወግ ኮፌ’

ለወትሮው ሰዎች፣ ‹‹እዚህ ካፌ እንገናኝ!››፣ ‹‹እዚህ ቡና ቤት ጎራ እንበል!›› ሲባባሉ ብዙውን ጊዜ መዝናናት የተሞላባቸው፣ ቀላል ሃሳቦችን ለመጋራት ከማለም እንደሆነ ይገመታል፡፡

በመሃል አዲስ አበባ በሚገኝ አንድ ለየት ያለ ካፌ ውስጥ የሚገናኙ ባለንጀሮች ግን ፣ከተለመደ ወግ የተሻገሩ፣ ህይወት የሚለውጡ ልምዶችን ይለዋወጣሉ፡፡

ጥንስስ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች በየዘርፉ ጥርሳቸውን ከነቀሉ አንጋፋወች ጋር ተገናኝተው መንገዳቸውን ያቃናሉ፣ ከሃሳብ መሰሎቻቸው ጋር ትስስር ይፈጥራሉ፣ንግድ እና ምጣኔ ሀብትን የሚመለከቱ መላዎችን ሲፈቱ ሲቋጩ ይውላሉ፡፡

ከተከፈተ 10 ወራትን ያስቆጠረው የ‹‹ቁምነገር ›› ቡና ቤት "ወግ ኮፊ" ይሰኛል፡፡ሀብታሙ ስዩም አጭር ቅኝት አድርጓል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ወግ ኮፌ፣ ቁምነገር እና ቡና