ዋሽንግተን ዲሲ —
በርካታ የፖለቲካ እና ህሊና እስረኞች ይቀርቡባቸው በነበሩባቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ 4ተኛ እና 19ኛ ምድብ ችሎቶች ቤተኛ የሆኑ አዛውንት አሉ።
ሰልባጅ ክራባት አንገታቸው ላይ ያሰሩ(በእሳቸው አነጋገር)፣ ጠብደል መዝገቦች ከእጃቸው የማይጠፉት እኒህ ሰው ወንድሙ ኢብሳ ይባላሉ።
ስራቸው ጥብቅና ነው።ያኔ ቀን ከቀን ተጠርጣሪዎች እና ፍርደኞች የልደታን ቅጽር ሲያዘወትሩ ፣ጠበቃ ይቀጥሩበት ገንዘብ የሌላቸው እስረኞች በዐይናቸው ይፈልጓቸዋል ፤ እሳቸውም ገንዘብ ያላቸውም ብለው መሸሽ የሚያውቁ አይመስሉም ።
ከ600 በላይ ለሆኑ የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች “ከለውጡ በፊት” ጥብቅና ቆመውላቸዋል።ይኼን ማድረጋቸው ግን ህይወታቸውን ለአደጋ ማጋለጡ፣ የእንግልት መምዘዙ አልቀረም።
ሙሉ ጥንቅሩን ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
ከ600 በላይ ለሆኑ የፖለቲካ እና ህሊና እስረኞች ጥብቅና የቆሙት ወንድሙ ኢብሳ ማን ናቸው?