ዋሽንግተን ዲሲ —
የህዝባዊ ወያነ -ሐርነት ትግራይ ልሳን የሆነው ወይን መጽሄት ከሰሞኑ ያወጣው ጽሁፍ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል።
ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫን በተመለከተ በመጽሄቱ ላይ በታተመው ጽሁፍ ፣ ቀጣዩ ምርጫ ከተራዘመ «ሊከሰት የሚችለውን የህጋዊ ቅቡልነት ችግር (legitimacy crisis) ለማስወገድ» በትግራይ ምርጫ ማካሄድ እና ክልሉ «በአንጻራዊነት ነጻ የሆነና የተሟላ መንግስታዊ መዋቅር (Institution) ያሉት እና የገነባ ፣ በአንጻራዊነት ሲታይ ራሱን የቻለ ክልል (Defacto State) » መሆን የሚችልበት ስራ መስራት ወሳኝ መሆኑን ተጠቁሟል።
ይሄን ከሰሞኑ ሲያነጋግር የሰነበተ ጉዳይ በተመለከተ ሀብታሙ ስዩም በክልሉ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች እና የህወሐት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልን ሀሳብ ጠይቋል።እንደሚከተለው ይደመጣል።
Your browser doesn’t support HTML5
በህወአት ልሳን ላይ የወጣውን አነጋጋሪ ጽሁፍ በተመለከተ በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ምን ይላሉ?