ግጭቱ የተካሄደው በን ጉዌራንዴ በተሰኘችው ደቡባዊ-ምሥራቅ ከተማ ውስጥ ሲሆን፣ በዚሁ ወቅት ቢያንስ አራት ሲቪሎችና አንድ ወታደር መሞታቸውን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
የቱኒዝያ ወታደሮች፣ ከሊብያ ጋር በሚዋሰነው ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ አንድ የፓሊስ ጣቢያና አንድ የጦር ካምፕ ላይ ጥቃት ያካሄዱ 21 ነውጠኞችን እንደገደሉ፣ የቱኒዝያ አገር ውስጥ ሚኒስቴር ዛሬ ሰኞ አስታወቀ።
ግጭቱ የተካሄደው በን ጉዌራንዴ በተሰኘችው ደቡባዊ-ምሥራቅ ከተማ ውስጥ ሲሆን፣ በዚሁ ወቅት ቢያንስ አራት ሲቪሎችና አንድ ወታደር መሞታቸውን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
የተኩስ ልውውጡ እንደጀመረ የአካባቢው ነዋሪዎች ከቤቶቻቸው እንዳይወጡም ባለሥልጣንቱ አሳስበዋል። ሊብያ ውስጥ፣ እራሱን እስላማዊ መንግሥት የሚለውን በድን ጨምሮ አማጽያን
በመበራከታቸው፣ የቱኒዝያ ኃይሎች በምዕራባውያን ወታደሮች እየታገዙ እንደሆነም ይታወቃል። አጭር የዜና ዘገባውን ለማዳመጥ ከዚህ በታች ያለውን የድምጽ ፋይል ያድምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
የቱኒዝያ ወታደሮች በፓሊስ ጣቢያና በጦር ካምፕ ላይ ጥቃት ያካሄዱ 21 ነውጠኞችን እንደገደሉ አስታወቁ
Your browser doesn’t support HTML5
VOA60 Africa - Tunisia: At least 30 militants killed