የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከትናንት በስተያ ለተወካዮች ምክር ቤቱ ጥምር ጉባዔ ያደረጉት ንግግር በተከታተሉት አሜሪካዊያን በአመዛኙ አዎንታዊ አቀባበል ማግኘቱ እየተሰማ ነው። ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ላይ መተባበርና የሁለቱንም ገዥ ፓርቲዎች የጋራ ውሣኔዎች መጠየቃቸው ብዙ ሪፐብሊካንን አስደስቷል።ዴሞክራቶቹ ግን በትረምፕ እውነተኛ አቋም ላይ ጥርጣሬአቸው እንደበረታ ነው።
ዋሺንግተን ዲሲ —
እጅግ ጎርበጥባጣ ከነበረውና ብዙ ድምፅ ከበዛበት የትራምፕ አስተዳደር የመጀመሪያ ዓመት በኋላ ፕሬዚዳንቱ ለእንደራሴዎች፣ ለሕዝባቸውም፣ ለዓለምም ያደረጉት ንግግር የሃገራቸውን የፖለቲካ ሰዎችና ዜጎቻቸውንም ለአንድነት የሚጣራ መልዕክት የጎላበት ነበር፡፡
ይህንን የተለሳለሰ የሚመስለውን የፕሬዚዳንቱን የንግግር ቃናና ከተቃዋሚው ፓርቲ ጋር አብሮ የመሥራት ጥሪ ሪፖብሊካኑ ወድደውታል፡፡
ዴሞክራቶቹ ግን ፕሬዚዳንቱ በተናገሩበት ጊዜ ሁሉ በአብዛኛው አላጨበጨቡላቸውም፡፡ በፕሬዚዳንት ትረምፕ ልባዊነት ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ነው በዚያ የጠቆሙት - ያመለካቱት።
ፕሬዚዳንቱ ከተናገሩ በኋላ የተወሰዱ የሕዝብ አመለካከት ናሙናዎች ለጊዜው የሚያሳዩት ግን ሰዉ ያንን መላዘባቸውን እንደወደደላቸው ነው፡፡ ቢያንስ ለጊዜው ያሰቡት የተሳካ ይመስላል፡፡
ጥያቄው ግን ይዘልቅ ይሆን? የሚል ነው፡፡
የተያያዙትን የድምፅና የቪድዮ ፋይሎች ይክፈቱ።
Your browser doesn’t support HTML5
ዶናልድ ትረምፕ በኮንግረስ ቃናቸው ይዘልቁ ይሆን?
Your browser doesn’t support HTML5
ዶናልድ ትረምፕ በኮንግረስ ቃናቸው ይዘልቁ ይሆን?