በአክሱም ሴት ተማሪዎች ሒጃብ እንዳይለብሱ የተደረገውን ክልከላ የሚቃወም ሰለፍ በመቐለ ተካሔደ

Your browser doesn’t support HTML5

በአክሱም ሴት ተማሪዎች ሒጃብ እንዳይለብሱ የተደረገውን ክልከላ የሚቃወም ሰለፍ በመቐለ ተካሔደ

የአክሱም ፍርድ ቤት እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ የአክሱም ሴት ተማሪዎች ሒጃብ እንዳይለብሱ የተጣለባቸው እገዳ እንዲነሳ ባለፈው ሳምንት ያሳለፉት ውሳኔ ባለመተግበሩ ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።

ሰልፉ “ሒጃብ ትለብሳለች ትምህርቷም ትማራለች” በሚል መሪ ቃል፣ በመቐለ ጎዳናዎች ከተካሔደ በኋላ በከተማዋ ማዕከል በኾነው ሮማናት አደባባይ ተጠናቋል።

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ፕሬዝዳንት ሸኽ አደም ዓብደልቃድር ጁሃር፣ “ከአንድ ሺሕ 400 ዓመታት በፊት መጠግያ ያጡ አማኞች ተቀብላ ባሰተናገደችው ትግራይ እንዲህ ማጋጡሙ አሳዛኝ ነው ብለዋል።

የሰልፈኞቹ ተወካዮች ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ጋራ ተወያይተዋል። አቶ ጌታቸው ለጥያቄው አፋጣኝ መፍትሄ ባለመሰጠቱ ይቅርታ ጠይቀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።