ዜና የሶማሊያው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተላለፈ ኖቬምበር 29, 2016 አሉላ ከበደ هزاران نفر از حامیان پرزیدنت ترامپ در شهر سینسناتی در ایالت اوهایو برای سخنرانی او حضور یافتند. اوهایو از ایالتهای کلیدی انتخابات ۲۰۲۰ است. پرزیدنت ترامپ در دور قبل با چهارصد هزار رای اختلاف هیلاری کلینتون را در این ایالت شکست داده بود. “አይበለውና ከአንዳች የቁማር መጫወቻ ሥፍራ ብሆን፤ ይህ ምርጫ እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን አቆጣጠር በ2012ዓ.ም. ከተካሄደውም ሆነ ከዚያ በፊት ከተካሄደው ይበልጥ የተበታተነችና ንቅዘት የተንሰራፋባት ሶማሊያን እንድትፈጠር ምክያት ይሆናል ብዬ ባለፉት ሰላሣ ዓመታት በሥራዬ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ ለውርርድ አቀርባለሁ፤ የሚታየው ሙስና በቃላት መግለጥ ከሚቻለው በላይ ነው።” በሜኔሶታ የሚኖሩ የሶማሊያ ተወላጅ ዋሺንግተን ዲሲ — የሶማሊያው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ነገ ረቡዕ ሊካሄድ ቀነ ቀጠሮ ተቆርጦ ቢያዝም የሙስናና ሌሎች ፈተናዎች ክሶች ሳቢያ ለሌላ ጊዜ ተላለፈ። ለመሆኑ ውሳኔው በጠቅላላው የምርጫ ሂደት ላይ ምን ዓይነት አንድምታ ይኖረው ይሆን? ወሰብሰብ ባለው የሶማሊያ የምርጫ ሥርዓት መሠረት የተለያዩ የጎሳ እና የየክልል ተወካዮች የሁለቱን ብሔራዊ ምክር ቤቶች ሃምሳ በመቶ አባላት ሲመርጡ፤ ቀሪው የሸንጎ አባላት ተመርጠው ውጤቱ እስኪታወቅ ድረስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫው አይካሄድም። በሶማሊያ ሕገ-መንግስት መሠረት የአገሪቱ የምክር ቤት አባላት የቀጣዩን የሶማሊያ ፕሬዝዳንት እስኪወስኑ ድረስ ገና ረዘም ያለ ጊዜ ሊወስድ ነው። ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ Your browser doesn’t support HTML5 የሶማሊያው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ተላለፈ