የላም ወተት የተዘጋጀ የጸጉር ቅቤን አሽጋ ለዓለም የምትሸጠው ኢትዮጵያዊት
Your browser doesn’t support HTML5
ወ/ሮ ገነት ስለሺ የፎቶግራፍ ባለሞያ ስትሆን ነዋሪነቷ በአሜሪካ ሃገር ነው፡፡ በዓመታት ከሃገር ውጪ ቆይታዋ ያጋጠማት የጸጉር መርገፍ፣ መጎዳት እና ተስማሚ የሆነ ምርት ማጣት ችግር 'ሹሩባ የጸጉር ቅቤ' የተሰኘ ከላም ወተት የተመረተ የጸጉር ቅቤ ማምረቻ ተቋም እንድትከፍት እና ለዘመናት የቆየው የኢትዮጵያዊያን ጸጉርን ቅቤ የመቀባት ባህል ከኢትዮጵያ ውጪም እንዲስፋፋ ማድረግ እንድትችል አድርጓታል፡፡