የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በቀድሞ ፓርቲያቸው ኦሕዴድ የአንድ ጊዜ ስጦታ ሊያበረክትላቸው እንደሆነ ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ። ይህ ውሳኔ እስካሁን ሲያነሱት ት ከነበረው የመብት ጥያቄ ጋ የሚገናኝ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንትና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የአንድ ጊዜ ስጦታ ሊያበረክትላቸው እንደሆነ ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ።
ከፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ በኩል የቤት መኪና እንዲገዛላቸው፣ የገንዘብ ስጦታ እንደሚበረከተላቸውና በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሕክምና ወጪያቸው እንዲሸፈንላቸው መወሰኑ ተነግሯቸዋል። ይህ ውሳኔ እስካሁን ሲጠይቁት ከነበረው የመብት ጥያቄ ጋ የሚገናኝ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
"በፕሬዝዳንትነቴ ላገኝ ከሚገባኝ ጋ የሚገናኝ አይደለም"- ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ