የወታደሩ ማስታወሻ ግለ ታሪክ

Kassa Gebremariam - a solider's story

“በአንድ ወቅት ልዩ ኃይል ያቋቋመ፤ የአውሮፕላን ጠለፋ በኢትዮጵያ ዓየር መንገድ የየዕለት ሥራ ላይ ከፍተኛ አደጋ በደቀነበት ወቅት የመጀመሪያውን የበረራ ደህንነት ተቋም የቆረቆረ እና በሬንጀር በዓየር ወለድ፥ በመረጃ ትምሕርትና ሌሎች የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት ዘርፎች የሰለጠነ፤ ተዋጊና በጦር ትምሕርት መምሕርነት ጭምር ያገለገለ ወታደር ነው።” የመጽሃፉ ደራሲ ዶ/ር ስንታየሁ ካሳ

Your browser doesn’t support HTML5

የወታደሩ ማስታወሻ .. ግለ ታሪክ .. ክፍል አንድ

Your browser doesn’t support HTML5

የወታደሩ ማስታወሻ .. ግለ ታሪክ .. ክፍል ሁለት

Your browser doesn’t support HTML5

የወታደሩ ማስታወሻ .. ግለ ታሪክ .. ክፍል ሦሥት

የጦር ባለታሪክ ናቸው። በንጉሰ-ነግስቱ ዘመነ መንግስት ከሶማሊያ ሰርገው በሚገቡ ኃይሎች ይፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶችን ለመግታት የልዩ ኃይል በማቋቋም፤ የጦር ትምሕርት ቤት በማደራጀት የሰሩትን ጨምሮ በበርካታ የጦር አውድማዎች ስለፈጸሟቸው የጦር ጀብዱዎች ይነገርላቸዋል።

የወታደሩ ማስታወሻ ግለ ታሪክ

በኢትዮጵያ ዓየር መንገድ የበረራ ደህንነትን በማቋቋምና ሌሎች የተለየ ግምት በሚሰጣቸው ሥራዎቻቸውም ይነሳሉ።

“ካሳ ገብረማሪያም” በሚል ርዕስ በስማቸው ተጽፎ ለሕትመት የበቃው መጽሃፍ በቅርቡ ነው፤ ከዋሽንግተን አቅራቢያ በምትገኘው የአርሊንግተን ከተማ ለአንባብያን የተዋወቀው። የግለ ታሪክ መጽሃፉ ደራሲ ልጃቸው ዶ/ር ስንታየሁ ካሳ ናቸው።