አዲስ አበባ —
ሐይቅ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጭና የመንግሥት ተቋማት በሙሉ በህወሓት ጉዳት እንደደረሰባቸው የከተማ አስተዳደሩ ተናግሯል።
በአሁኑ ወቅት ለሰዉ አገልግሎት መስጠት የሚችል ተቋም እንደሌለ የከተማዪቱ ምክትል ከንቲባ መሱድ አበራ ገልጸዋል።
ጉዳት ከደረሰባቸው ተቋማት አንዱ ከሆነው ሐይቅ ሆስፒታል “የህወሓት ታጣቂዎች መድኃኒቶችንና የህክምና መሣሪያዎችን ጨምሮ የሆስፒታሉን ንብረቶች ዘርፈው ሲወስዱ ማየታቸውን” አንድ የሆስፒታሉ ሃኪም ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችንና የተቋማት ውድመቶችን በተመለከተ የሚቀርቡባቸውን ክሦች፣ የህወሓት መሪዎች በተደጋጋሚ አስተባብለዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።
Your browser doesn’t support HTML5
ሐይቅ ከተማና ጉዳቷ