የሀዲያ ሚዲያ ዩቲይብ ባለቤት በሁለት ክስ ነፃ ሲባል አንዱን እንዲከላከል ተወሰነ

አቶ መለሰ አብርሃም የሀዲያ ሚዲያ ሀውስ ዩቱዩብ ባለቤት

በእስር ላይ የሚገኘው የሀዲያ ሚዲያ ሃውስ ዩቲዩብ ባለቤት አቶ መለስ አብርሀም ከቀረቡበት ሦስት ክሶች በሁለቱ "ነጻ" ሲባል ፣ ርእሰ መስተዳደሩ በመተቸት በሚለው በአንዱ ክስ እንዲከላከል ብይን ተሰጠ።

Your browser doesn’t support HTML5

የሀዲያ ሚዲያ ዩቲይብ ባለቤት በሁለት ክስ ነፃ ሲባል አንዱን እንዲከላከል ተወሰነ

የመከላከያ ምስክሮቹን እንዲያሰማም የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትላንት ታኅሣሥ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ባስቻለው ችሎት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ተከሳሹ በዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤት ቢወስንም፣ አኹንም በእስር ላይ እንደሚገኝ ወንድሙ ለአሜሪካ ድምጽ ገልጿል። ከክልሉና ከዞኑ ባለሥልጣናት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።