አሥረኛው የኢሕአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ዛሬ ጠዋት በመቀሌ ከተማ ተከፍቷል፡፡
መቀሌ —
ኢሕአዴግ
Your browser doesn’t support HTML5
ኢሕአዴግ ጉባዔውን እየካሄደ ነው
አሥረኛው የኢሕአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ዛሬ ጠዋት በመቀሌ ከተማ ተከፍቷል፡፡
በጉባዔው ላይ ከአራቱ የግንባሩ አባል ድርጅቶች የተወከሉ ከእያንዳንዳቸው 250 250 ሰው በጠቅላላው አንድ ሺህ አባላት በድምፅ እና 500 ያለድምፅ እየተሣተፉ ናቸው፡፡
በጉባዔው ላይ ንግግር ያደረጉት የግንባሩ ሊቀመንበር አቶ ኃይለማርያም ደሣለኝ ይህ የግንባራቸው ጉባዔ ሃገሪቱን በ2017 ዓ.ም (በመጭዎቹ አሥር ዓመታት ማለት ነው) መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ ለማሰለፍ የተያዘውን ራዕይ ዕውን ለማድረግ የሚያስችል የዕቅድ አቅጣጫ ያፀድቃል ብለዋል፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የግርማይ ገብሩን ዘገባ ያዳምጡ፡፡