በኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት የመሪዎች ምርጫ ሂደት፤ በወቅቱ የአገሪቱ መሪ ማንነትና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የተካሄደ ቃለ ምልልስ።
Your browser doesn’t support HTML5
በኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት ስብሰባ የግንባሩና የአገሪቱ መሪዎች ምርጫ
የኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት በያዝነው ሳምንት መገባደጂያ በሚያካሂደው ስብሰባ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የፓርቲውን ሊቀመንበርና የአገሪቱን ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊን የሚተካ መሪ ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በማእከላዊ ምክር ቤቱ ስብሰባና የምርጫ ሂደት፤ እንዲሁም ብዙዎችን ሲያነጋግር በሰነበተው በአገሪቱ ኅገ መንግስታዊ ድንጋጌ መሠረት አቶ መለስን በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚንስትርነት የተኩት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በመንግስት ብዙኃን መገናኛዎች በምክትል ጠቅላይ ሚንስርነት መጠራትና ሌሎች ተዛማች ርዕሶች ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዲሬክተር አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተካሄደ ቃለ ምልልስ ነው።