በኢንዱስትሪ የገፉት የቡድን ሃያዎቹ ሀገሮች ባለፈው ዓመት ፓሪስ ላይ የፈረሙት ስምምነት የሚያዝዘውን ግዴታ ለመወጣት የሚያስችሉ እርምጃዎችን ሳይወስዱ መቅረታቸውን የሚጠቅስ ሰሞኑን የወጣ ሪፖርት ውቅሷል፡፡
ዋሺንግተን ዲሲ —
በዚህ ላይ ተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በምረጡኝ ቅስቀሳቸው ወቅት ይዝቱ እንደነበረው ከፓሪስ ስምምነት የሚወጡ ከሆኑ በካይ ጋዞች ወደ ከባቢው አየር መልቀቅ ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረትና እየታየ ያለውን መነቃቃት፣ ሊያስተጓጓልና ሊቀለብሰው ይችላል፤ ሲሉ የአየር ንብረት ጉዳይ ተመራማሪዎች ሥጋታቸውን እያሰሙ ነው፡፡
የስምምነቱ ፊርማ ከሆኑትና ግምባር ቀደም በካይ ከሚባሉት ሀገሮች መካከል የዩናይትድ ስቴትስ፣ አርጀንቲና፣ አውስትራሊያ፣ ካናዳ፣ ሳዑዲ አረቢያና ቱርክ በቅነሳው የሚጠበቅባቸውን ለመምታት የሚያስችላቸውን ሕግጋት ሳያወጡ መቅረታቸው አነጋግሯል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
Your browser doesn’t support HTML5
የፓሪስ ስምምነት ዕጣ ፋንታ