የዛሬይቱን ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ አያያዝ በመርመር መቀጣዩ ምዕራፍ "ሊሆን ይገባዋል" ያሉትን በማስፈር የለውጡን አቅጣጫ በየበኩላቸው የቃኙ ሁለት የፖለቲካና የምጣኔ ሃብት አዋቂዎች ናቸው በቅርቡ ይፋ ያደረጓቸውን ፅሁፎች መሠረት ባደረገ ዝግጅት የሚከራከሩት::
የመጀመሪያው ፀሃፊ ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ የአፍሪቃ የስትራተጂያዊና የፀጥታ ጉዳዮች ተቁዋም ሥራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር ናቸው:: በቀደመው ወታደራዊ መንግሥት በሲቪል አስተዳደር እና በወታደራዊ ሞያ በተለያዩ ከፍተኛ ኃላፊነቶች አገልግለዋል::
ሁለተኛውፀሃፊዶ/ር ዮናስ ብሩ በዓለም ባንክ ዓለም አቀፍ የንፅፅር ፕሮግራም ምክትል ሥራ አስኪያጅ በመሆን ያገለገሉ አንጋፋ የምጣኔ ኃብት ባለሞያ ናቸው:: በአምስት ቋንቋዎች በየሶስት ወሩ የሚታተመው የዓለም ባንክ የጥናት መፅሄት ዋና አዘጋጅ በመሆንም አገልግለዋል:: በቅርቡም ኢትዮጵያ ለምን ገለልተኛ የምጣኔ ሃብት አማካሪዎች መማክርት ማቋቋም እንደሚያስፈልጋት የሚሞግት አንድ ጥናታዊ ሰነድ ከሌሎች የሞያ አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በተባባሪነት አዘጋጅተዋል::
የክርክራቸውን ፍሬ ነገሮች ከዚህ ይከታተሉ::
Your browser doesn’t support HTML5
የነገይቱ ኢትዮጵያ መጭ ጊዜያት መንታ መነፅሮች - ክፍል አንድ
Your browser doesn’t support HTML5
የነገይቱ ኢትዮጵያ መጭ ዕጣ ሲቃኝ
Your browser doesn’t support HTML5
የነገይቱ ኢትዮጵያ መጭ ጊዜያት በመንታ መነፅሮች ሲቃኝ