ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በችግሮቿ ዙሪያ እንደምትሠራ አስታወቀች

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በችግሮቿ ዙሪያ እንደምትሠራ አስታወቀች

በኢትዮጵያ ያለውን ችግር ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር ለመፍታት መንግሥት ዝግጁ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።

ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው 39ኛው የአፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መደበኛ ስብሰባ ላይ አቶ ደመቀ መኮንን ባደረጉት ንግግር፣ በሀገሪቱ ያለውን ችግር ከአፍሪካ ሕብረት ጋር በመተባበር ለመፍታት መንግሥታቸው ዝግጁ መሆኑን እንዳብራሩ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

ስብሰባው በአፍሪካን የበጀት ጉዳይ፣ በኮቪድ-19ና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ የስብሰባውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት፣ የህብረቱ በጀት በራሷ በአፍሪካ ሊሸፈን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡