አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ

ባለፈው ሰኞ ሌሊት፣ ከምትኖርበት ሕንፃ አምስተኛ ፎቅ ላይ ቁልቁል ወድቃ ሕይወቷ ካለፈው፣ ሞዴል እና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ ሞት ጋራ በተያያዘ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር የሚገኘው እጮኛዋ አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ፣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር ቆይቶ ምርመራ እንዲቀጥል ፍርድ ቤት አዘዘ።

የዐዲስ አበባ ፖሊስ፣ ከቀነኒ ሞት ጋራ በዋና ወንጀል አድራጊነት የጠረጠረው አንዱዓለምን እንደኾነ በመግለጽ፣ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቆ የነበረ ሲኾን፣ ከጠበቃው ጋራ ፍርድ ቤት የቀረበው አንዱዓለም ደግሞ፣ የቀነኒ ሕይወት ያለፈው በአደጋ እንደኾነ በመግለጽ ከእስር እንዲፈታ አመልክቶ ነበር።