“ሁለት አቅጣጫ የያዘ ጥቃት ነው። አንደኛው .. በጀነራል ሰዓረ ላይ የተቃጣው .. በኢትዮጵያዊነት ላይ። ሁለተኛው ዶ/ር አምባቸው መኮንን የደረሰው .. በማዕከላዊነት ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው።” ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ።
“ይሄ ጥቃት ኢትዮጵያዊነትን ይበልጥ አጠናክሮ መሄድ አለበት ብዬ ነው የማነው። .. ‘ከዚህ ምን እንማራለን?’ .. ‘እንዳይደገምስ ምን መደረግ አለበት?’ የሚለው ተጠናቅሮ መቀጠል አለበት የሚል ዕምነት አለኝ።” አቶ ክቡር ገና።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የአገሪቱን የኤታማዦር ሹም ጨምሮ አምስት ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል መንግሥት ባለ ሥልጣናት የተገደሉበትና ሌሎች የቆሰሉበት ጥቃት አሁንም እያነጋገረ ነው። የግድያውን አንድምታና ቀጣዩን አቅጣጫዎች ለሚመረምር በታለመ የትንታኔ ውይይት ሁለት የኢትዮጵያ ጉዳይ አዋቂዎች ይነጋገራሉ።
ተወያዮቹ፡- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው የፍልስፍና መምሕሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ እና የኢንሽዬቲቭ አፍሪካ ሥራ አስፈጻሚ ዳይሬክተር አቶ ክቡር ገና ናቸው።
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
የመሰንበቻው የባለሥልጣናቱ ግድያ እና አንድምታ