Your browser doesn’t support HTML5
አማራ ክልል ዳውንት ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ 25 ሰዎች ሞቱ
ከአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ መለስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ገደል ውስጥ ገብቶ 25 ሰዎች መሞታቸውን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡
በፋኖ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ነው የተባለውና አደጋው የደረሰበት የዳውንት አካባቢ ነዋሪዎችና የዳውንት ወረዳ መናኻሪያ አስተባባሪ ስምሪት ባለሞያ የሟቾን ቁጥር እስከ 30 ከፍ ያደርጉታል።
አደጋው በደረሰበት አካባቢ የሚገኙት ሁለት ጤና ጣቢያዎች በአደጋው የሞቱና ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ ጤና ተቋማቱ መምጣታቸውን አረጋግጠው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው 16 ሰዎች ወደ ደላንታ ሆስፒታል መላካቸውን አመልክተዋል፡፡አድማጮች ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።