ምርጫ 2012 - የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ክርክር ሲተነተን፤

Presidential Debate

የክርክር ተጨባጭ ሚናና ይዘት፤ እንዲሁም በፕሬዝዳንት Obama እና በተፎካካሪያቸው Mr Romney መካከል የተካሄደው የመጀመሪያው ዙር ክርክር ይፈተሻል።

Your browser doesn’t support HTML5

ምርጫ 2012 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ክርክር ትንታኔ


በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ከፍ ያለ ግምት ተሰጥቶት ሲጠበቅ የቆየው የ2012ቱ የመጀመሪያ ዙር ክርክር በትላንትናው ምሽት በደቡብ ምእራቧ የኮሎራዶ ክፍለ ግዛት የዴንቨር ከተማ ተካሂዷል።

ለመራጩ ኅዝብ ውሳኔ ያግዝ ዘንድ ክርክሩ ትኩረት ባደረገባቸው ርእሰ ጉዳዮች «የትኛው እጩ ምን ዓይነት አማራጭ አቀረበ? ለመሆኑስ ይህን መሰሉ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ክርክር ምን ዓይነት ተጨባጭ ጠቀሜታ ይኖረው ይሆን?» የሚሉትን ጨምሮ በክርክሩ ይዘትና መሠረቶች ላይ የቀረበ ትንተና ነው።

ሞያዊ ትንታኔውን የሰጡት፥ ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማሪያም በሳንበርናንዲኖው የካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህርና የኅግ ባለ ሞያ ናቸው።