ትግራይ ክልል ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚነት ጥሪ አቀረበ

Your browser doesn’t support HTML5

ትግራይ ክልል ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚነት ጥሪ አቀረበ

አፍሪካ ኅብረት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚነት ትኩረት እንዲሰጡ የትግራይ ክልል ጥሪ አቀረበ።

የፕሪቶሪያውን ስምምነት አጠቃላይ ሂደት እና ከሂደቱ ተገኙ የተባሉ ትምህርቶችን በተመለከተ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ይፋ ተደርጓል።

ሪፖርቱ ይፋ በኾነበት ወቅት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ባቀረቡት ጥሪ፣ እስካሁን አልተፈጸሙም ያሏቸው የስምምነቱ ነጥቦች እንዲፈፀሙ የአፍሪካ ኅብረትና እና ዓለምዓቀፉን ማኅበረሰብ ትኩረት ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በበኩላቸው፣ ቀጣይ ሂደቶች በውይይትና ሕግን ባከበረ መልኩ መተግበር አለባቸው ብለዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።