አዲስ አበባ ላይ ዛሬ የተከበረው የጥምቀት በዓል

Your browser doesn’t support HTML5

አዲስ አበባ ላይ ዛሬ የተከበረው የጥምቀት በዓል

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ዐበይት በዓላት አንዱ የሆነውና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት /ዩኔስኮ/ የተመዘገበው የጥምቀት በዓል ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በድምቀት ተከብሯል። በዓል ከሚከበርባቸው ቀደምት ቦታዎች አንዱ ጃን ሜዳ ሲኾን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በተገኙበት፣ የጥምቀት ሥነ-ስርዐቱ ተከናውኗል፡፡

ፓትሪያርኩ በንግግራቸው፣ የሰላም ጥሪ አቅርበዋል። የእምነቱ ተከታዮች እና ጎብኚዎችም አስተያየት ሰጥተውናል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።