ዩናይትድ ስቴትስ 453 ሺ ፀረ ኮቪድ 19 ክትባት ለኢትዮጵያ ለግሳለች
Your browser doesn’t support HTML5
ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የለገሰችውን 453 ሺ ፀረ ኮቪድ 19 ክትባት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ለጤና ሚንስቴር አስረክበዋል። ልገሳው የተደረገው የጆ ባይደን አስተዳደር ከኮቫክስ ጋር በጥምረት ከለገሰው 25 ሚሊየን የሚጠጋ ክትባት መካከል መሆኑ ነው አምባሳደሯ ገልፀዋል ።