ይህ መተግበሪያ የኢትዮጵያዊያንን የእንስሳት ግብይት ልምድ ይቀይር ይሆን?

YERAS GEBYA

ለወትሮው ከብት ለመግዛት የሚፈልግ ሰው፣ ወደ ልማዳዊ የከብት መሸጫ ስፍራዎች ማቅናት ፣እግር እስኪዝል ማማረጥ ፣ ጉሮሮ እስኪደርቅ የዋጋ ክርክር ማድረግ ይጠበቅበት ነበር። ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች የጀመሩት አውታር ግን ይሄንን ልማድ ለማስቀረት ያለመ ይመስላል።

የራስ ገበያ የተሰኘው የበይነ መረብ ላይ የእንስሳት ግብይት አውታር፣ በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ሸማቾች እና ሻጮች ሁሉን ነገር "ኢንተርኔት" ላይ ጨርሰው እንስሳቱን እንዲረካከቡ የሚያደርግ መሆኑን መስራቾቹ ይናገራሉ።

ከሀብታሙ ስዩም ጋር አጭር ቆይታ ያደረገው የራስ ገበያ ተባባሪ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ መስፍን አበራ ስለ በይነ መረብ ላዩ የእንሳት ገበያ ያስረዳናል።

Your browser doesn’t support HTML5

ይህ መተግበሪያ የኢትዮጵያዊያንን የእንስሳት ግብይት መንገድ ይቀይር ይሆን?