የ “መፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ” በባሕር ዳር
Your browser doesn’t support HTML5
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ። በክልልሉ ዛሬ በተደራጀ ሁኔታ በመንግሥት መዋቅር ላይ ጥቃት ለመሠንዘር መሞከሩን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅሕፈት ቤት የፕሬስ ኃላፊ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ማምሻውን ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።