“የቴሌቭዥን ድራማዎች የታሪክ ጭብጥና የገጸ ባሕሪያት አሳሳል ትውልድን አምካኝ ናቸው” ባለሞያዎች

Your browser doesn’t support HTML5

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እና በኢቢኤስ ቴሌቭዠን ጣቢያዎች ላይ ከዘጠኝ በላይ ተከታታይ የቴሌቭዠን ፕሮግራሞች በመተላለፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ድራማዎቹ በከፍተኛ ሁኔታ አብዛኛውን የኅብረተሰብ ክፍል እይታ የተቆጣጠሩ ናቸው፡፡ በእነዚህ በብዛት እየቀርቡ ባሉ የቴሌቭዥን ድራማዎች የታሪክ ጭብጥና የገጸ ባሕሪያት አሳሳል ለትውልድ የሚተላለፈው መልዕክት ምንድነው? በሚል መጠይቅ የሚንደረደረው የዛሬው የትንታኔ ፕሮግራም ባለሞያዎችን አካቶ ይዟል፡፡አዘጋጇ ጽዮን ግርማ ነች፡፡