በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ነጋዴዎች በተደጋጋሚ ለዝግጅት ክፍላችን ሲናገሩ የቀን ገቢ ግምቱ በጣም የተጋነነ እንደሆነ በመግለጽ "ፍትሐዊ አይደለም" ብለውታል።
ጽዮን ግርማ የነጋዴዎቹ አቤቱታ ይዛ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋን አነጋግራለች።
አድማጮች የአዲስ አበባ ነጋዴዎችን በተመለከተ በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለሥልጣን የአዲስ አበባ የታክስ ፕሮግራም እና ልማት ሥራዎች ዘፍር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ነጻነት አበራ ለማግኘት ተደጋጋሚ ጥረት አድርገን እሳቸው ለጊዜው እንደሌሉ ተነግሮናል። ያናግሯችኋል የተባልነውን ተወካይም በዛሬው ዕለት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም በነገው ዕለት ይዘን ለመመለስ ጥረት እናደርጋለን።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ