በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በነጋዴዎች አቤቱታ ዙሪያ ከአቶ አዲሱ አረጋ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ


የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ

አዲሱ የቀን ገቢ ግምት በነጋዴዎችና በግብር ሰብሳቢው መካከል የፈጠረው አለመግባባት አሁንም እንደቀጠለ ነው። የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነጋዴዎች በተደረገው ግምት ላይ ተቃውሞና አቤቱታ እያቀረቡ ሲሆን በአቤቱታዎቹ ዙሪያ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋን አነጋግረናቸዋል።

በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ነጋዴዎች በተደጋጋሚ ለዝግጅት ክፍላችን ሲናገሩ የቀን ገቢ ግምቱ በጣም የተጋነነ እንደሆነ በመግለጽ "ፍትሐዊ አይደለም" ብለውታል።

ጽዮን ግርማ የነጋዴዎቹ አቤቱታ ይዛ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋን አነጋግራለች።

በነጋዴዎች አቤቱታ ዙሪያ ከአቶ አዲሱ አረጋ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ
please wait

No media source currently available

0:00 0:16:23 0:00

አድማጮች የአዲስ አበባ ነጋዴዎችን በተመለከተ በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለሥልጣን የአዲስ አበባ የታክስ ፕሮግራም እና ልማት ሥራዎች ዘፍር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ነጻነት አበራ ለማግኘት ተደጋጋሚ ጥረት አድርገን እሳቸው ለጊዜው እንደሌሉ ተነግሮናል። ያናግሯችኋል የተባልነውን ተወካይም በዛሬው ዕለት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም በነገው ዕለት ይዘን ለመመለስ ጥረት እናደርጋለን።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG