ሀዋሳ —
በኮሮናቫይረስ ምክንያት ከአነስተኛ የንግድ ሥራዎች በተጨማሪ ባለኮከብ ሆቴሎችም ከመቀዛቀዝ እስከመዘጋት መድረሳቸውን የሆቴሎቹ ኃላፊዎች ለቪኦኤ ገልፀዋል።
ከአገልግሎት፣ እንዲሁም ከሃገር ውስጥና ከውጭ ጎብኚዎች በሚገኝ ገቢ ላይ የተመሠረቱት የምጣኔ ኃብትና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳታቸውን የከተማይቱ አስተዳደር አስታውቋል።
የተቀዛቀዘውን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት መፍትኄ ጠቋሚ ጥናትና የማሻሻያ መርኃግብር እየተዘጋጀ መሆኑን የሃዋሳ ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።